2014 ጁላይ 13, እሑድ

ምሥጢረ ሥላሴ

ቅድስት ሥላሴ

በዚህ ሥር ስለ ቅድስት ሥላሴ (ግዚአብሔር - ብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ) ሦስትነትና አንድነት
ንማራለን፡፡ ሥላሴን ቅድስት ብለን የምንጠራው ሴት ልጅ ወልዳ እንደምታስገኝ ሥላሴ ዓለማትን ፈጥረው
ስላስገኙ ነው፡፡
ብዙዎች ስለ ቅድስትሥላሴ ያለውን ትምህርት እየሰሙ በእውነት ክርስቲያኖች በአንድ አ ምላክ ያምናሉ?
የሚያምኑስ ከሆነ አብ፣ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለት ምንድር ነው? ብለው ይጠይቃሉ፡፡
በተዛባ ግንዛቤም የተነሳ አንዳንድ ሰዎች ክርስቲያኖች ብዙ አማልክትን ያመልካሉ ብለው ይከሳሉ፡፡ የዚህም
ምንጩሥላሴየሚለውን ሦስት አማልክት ብለው ማሰባቸው ነው፡፡
በክርስትና እምነት ይህ የተሳሳተ መለካከት ነው፡፡ በክርስትና ምነት በብዙ አማልክት (Polytheism) ማምለክ
የተከለከለ ነው፡፡
የክርስት ና እምነት ማዕከሉ በአንድ አምላክ ማመን (Monotheism) ነው፡፡
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን የሱስ ክርስቶስከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ።እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ
ምላካችን አንድ ጌታ ነው፥አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም አሳብህ በፍጹምም ኃይልህ
ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት። ፊተኛይቱ  ትእዛዝ ይህች ናት።ማር 1229-30፡፡ ብሎ ነግሮናል፡፡
ብዙዎቻችን ተተንትኖ ከተዘጋጀው ሥነ መለኮታዊ ጥናት ይልቅ ለጊዜያችን በሚመጥን መልኩ ተስተካክሎ
አጠር መጠን ብሎ የቀረበን አ ስተምህሮ እ ንፈልጋለንና በዚህ ጭር ትምህርት የምንማረውም ስለ ሥላሴ
-ግዚአብሔር ራሱን ለሰው ከገለጠበት አንጻር በመመልከት ነው፡፡
ግዚአብሔርን የሚመስለው ማንም የለም፡፡እግዚአብሔር በኢሳይያስ ንደበትኔ አምላክ ነኝና፥ ሌላም የለምና የቀድሞውን የጥንቱን ነገር አስቡ እኔ እግዚአብሔር ነኝ እንደ እኔም ያለ ማንም የለም። 469 ብሏል፡፡
ግዚአብሔር በሁሉ ነገር የተለየ የሚተካከለው የሌለ ነው፡፡ንግዲህ እተካከለው ዘንድ በማን መሰላችሁኝ?
ይላል ቅዱሱ። 4025፡፡
ዓለምን ሁሉ በውስጣቸው የሚገኘውንም ሁሉ የፈጠረ የሚመስለው የሌለ እግዚአብሔር ነው፡፡በመጀመሪያ
ግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።ዘፍጥ 11፡፡እርሱንም የሚመስለው የለም፡፡
ግዚአብሔር ከሰው ችሎታና ግምት የላቀ የመጠቀ ነው፡፡
የእኛ በሆነው ጠባብ አእምሮ በተዳሰሰ ጥቂት ማብራሪያ እርሱንና መለኮታዊ አምላክነቱን ገልጦ ማስረዳት
አይቻልም፡፡
የእግዚአብሔር ሀሣቡ፣ መንገዱ፣ ዓላማው (ቅዱ) የሰው ከሆነው የተለየ ነው፡፡ሳቤ እንደ አሳባችሁ
መንገዳችሁም እንደ መንገዴ አይደለምና ይላል እግዚአብሔር፦ ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፥ እ ንዲሁ መንገዴ
ከመንገዳችሁ አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለ ነው። 558-9 ንዳለ፡፡
ስለእ ግዚአብሔር የምናውቀው ወይም ያወቅነው የገለጠልንን ያህል ብቻ ነው፡፡ ስለ እግዚአብሔር ሁሉንም
ነገር የምናውቅ አይደለንም፡፡
ግዚአብሔር አማላካችን ስለ ራሱ ያልገለጠልን ምስጢራት አሉ፡፡ ሊቀ ነቢያት ሙሴምሥጢሩ ለአምላካችን
ለእግዚአብሔር ነውየተገለጠውግን የዚህን ሕግ ቃሎች ሁሉ እናደርግ ዘንድ ለ እኛ ለዘላለምም ለልጆቻችን ነው።
ዘዳግ 2929፡፡
በዙሪያችን ከሚገኙ ነገሮች ሁሉ የተለየ ከመሆኑ የተነሳ ስለ ርሱ በሰው ቋንቋ መናገርና ማስረዳት ከባድ ነው፡፡
ስለዚህ መለኮታዊ ነገርን ለማስረዳት ምሳሌዎችን መጠቀም ግድ ይሆናል፡፡ ጌታችንአ ምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ በትምህርቱ በርካታ ምሳሌዎችን ተጠቅሞ አስተምሯል፡፡ ቅዱስ ማቴዎስ እንደተናገረው ቢያንስ አንድ ምሳሌ
ሳይጨምር አልተናገረም ነበር፡፡የሱስም ለሕዝቡ ይህን ሁሉ በምሳሌ ተናገረ፤ በነቢዩም። በምሳሌ አፌን እከፍታለሁ፥
ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የተሰወረውንም እናገራለሁ የተባለው ይፈጸም ዘንድ ያለ ምሳሌ አልተናገራቸውም።ማቴ 1334፡፡
ነዚህ ምሳሌዎች ከሰማእያኑ የዘወትር ሕይወት የመነጩ ናቸው፡፡ ስለ መለኮት የሚነገረውን እውነት የሚመስሉ
ምሳሌዎች ወይም ማስረጃዎች ተሰጥተዋል፡፡ ይህም በግድግዳ ላይ ያለ ሥዕልን እንደ መመልከት ነው፡፡ ሥዕሉ
ተፈጥሮን በቀጥታ የምንመለከትበት ባይሆንም ተፈጥሮን ግን ወክሎ መስሎ ያቀርባል፡፡ የሚወርድ ውሃ በሥዕሉ ላይ
ብንመለከት ለመጠጣት እጃችንን አንዘረጋም፡፡
ምሳሌ እንደ ሥዕሉ እውነትን ለማስረዳት ይቀርባል፡፡ ምሳሌ እውነቱን ለማስረዳት በጽሁፍም ሊቀርብ ይችላል፡፡ ነገር
ግን እውነቱ አሁንም ከማንኛውም ምሳሌ በላይ ነው፡፡
ውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ፡፡ዮሐ 151-27 በማለት ጌታችን የተናገረውየእውነተኛ የወይን ግንድምሳሌ
ለቅድስት ሥላሴ ጥሩ ምሳሌ ሆኖ ሊቀርብ ይችላል፡፡ ሙሉውን ምዕራፍ ስናነብ ስለ ሦስቱም አካለት ያስተማረውን
ትምህርት እናገኛለን፡፡
የተለያየ ዓይነት ዛፎች ስለሚገኙበት አንድ የአትክልት ሥፍራ እናስብ፡፡አንዳንዶቹ ሥራቸው ከመሬት ጠልቆ የገቡ
የተፈጥሮ ዛፎች ናቸው፤ ሌሎቹ ደግሞ ለአካባቢ ወይም ለቤት ማሳመሪያ እንዲሆኑ የተሠሩ ሥር የሌላቸው ሰው
ሠራሽ ዛፎች ናቸው፤ ቀጥሎ የሚገኙት ዛፎች ደግሞ ቅርንጫፎች ቢኖሩአቸውም ሥር ግን የሌላቸው ናቸው፤
በማስከተልም ያሉት ከፕላስቲክ የተሠሩ ዛፎች ሲሆኑ በእነዚህ ሁሉ መካከል ግን እውነተኛ የወይን ዛፍ ይገኛል፡፡
በዚህ በአእምሮ በታሰበ የአትክልት ሥፍራ እውነተኛውን ዛፍና ጥራቱን እንዴት ለይተን መወቅ እንችላለን?
ወይም እውነተኛውዛፍ ራሱን እንዴት አድርጎ መግለጥ ይችላል? ዛፉ ምንነቱንና ጥራቱን ለይተን ማወቅ
ንዲያስችለን ራሱን የሚገልጥበት መንገድ ሊኖረው ያስፈልጋል፡፡
ዛፍ ብቻ ሳይሆን ማንኛውም በዚህ ዓለም የሚገኝ ቁሳዊ ነገር ራሱን የሚገልጥበት መንገድ አለው፡፡ ለምሳሌ
ፀሐይን ብንወስድ መኖርዋን በሚያረጋግጡላት ነገሮች (በክበቧ፣ በብርሃንዋና በሙቀትዋ) ማካኝነት ፀሐይ
ስለመኖርዋ እንናገራለን፡፡ በነዚህም ወሳኝ በሆኑ መገለጫዎቿ አ ማካኝነት ፀሐይ ስለመኖርዋና ስለ ተጽእኖዋ
ግልጽ ታደርጋለች፡፡እ ነዚህ ሦስቱም በሁሉ ዘንድ የምትታወቅ የአንዲት ፀሐይ መገለጫዎች ናቸው፡፡
ነዚህም ሦስቱ የፀሐይ መገለጫዎች ባይኖሩ ፀሐይ ሐሳብ ብቻ የምትሆን ወይም የለችም ተብላ የምትቆጠር
ነበረች፡፡
ንደዚሁ ስለ ግዚአብሔር መኖርና እንሰማለን ናነባለንም፡፡ ይህ እውነት ግን እግዚአብሔር ራሱን
ባይገልጥ ኖሮ ተራ ሐሳብ ወይም አጠራጣሪ እምነት ይሆን ነበር፡፡
ግዚአብሔር ራሱን የገለጠበትና የሚገልጥበት የራሱ ብቻ የሆኑ ብቸኛ መንገዶች አሉ፤ ስለ ቅድስት ሥላሴ
የምንለውም እውነት ዋና ምንጭም ይኸው ነው፡፡
ስለ ሥላሴ በማወቅና በመረዳት እግዚአብሔር አለ እ ንላለን፡፡
ግዚአብሔር ራሱን ብቸኛ በሖነ መንገድ ገልጧል፡፡

ስለዚህ ስለ ቅድስት ሥላሴ ከቅዱሳት መጻሕፍት በምናደርገው ፍለጋ የሚከተሉትን ንመለከታለን፡፡ይቆየን
ምንጭ፡-ዘኦረቶዶክስ ድረ ገጽ

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ