2014 ኦገስት 2, ቅዳሜ

ዮሴፍ ፃድቅ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ


አምላክ አሜን!





እንኳን ለቅዱስ ዮሴፍ በዓለ እረፍት በሠላም አደረስዎት!

   
      አባቱ ያዕቆብ እናቱ ደግሞ ዮሐዳ ትባላለች፡፡ ቅዱስ ዮሴፍ   የእንጨት   ስራ   ባለሞያ  ስለነበር  ቤተሰቡን ያስተዳደር የነበረው በዚህ ስራው ነው ፡፡ በዚህም  የተነሳ ጠራቢው ዮሴፍ  በማለት  አይሁድ  ብዙ  ጊዜ  ስሙት ይጠሩት እንደነበር መፅሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡
     የአራት  ወንዶችና  የሦስት  ሴቶች  ልጆች  አባት ነው፡፡ ማቴ.13፡55 አረጋዊው  ከእመቤታችን  ከቅድስት ድንግል  ማርያም   ጋር   ያለውን   የሥጋ   ዝምድና ስንመለከት፡፡       
 አልዓዛር ማታንነናቅስራነን ወለደ ማታን ያዕቆብን ያዕቆብ ዮሴፍን ወለደ ቅስራ ደግሞ  እያቄምን እያቄም ማርያምን ወለደ፡፡
                                    
     አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ ከ1985 አረጋዊያን  መካከል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ለማገልገል በ84 ዓመቱ ተመረጠ፡፡
የተመረጠውም በሦስት ምስክርነት ነው፡-
1.  በትሩ አብባና  አፍርታ  የእመቤታችን  ጠባቂ  እሱ እንደሆነ ተፅፎባት በመገኘቱ፡፡
2. ርግብ በተለየ ሆኔታ በአረጋዊው በቅዱስ ዮሴፍ  ላይ በማረፏ
3. ዕጣ  ቢያወጡ  ለአረጋዊው  በመውጣቱ  ምክንያት ነው፡፡
    የአምላክን    እናት    ለማገልገልና      በድንጋይ ከመወገር   እንዲጠብቃት    የተመረጠው    አባታችን ቅዱስ ዮሴፍ   በእርጅናው  ወራት   ደከመኝ   ሰለቸኝ ሳይል  አገልግሏል፣  በስደት  ጊዜ  በበርሃ  ተንከራቷል፣ አምላኩን   እንደ   አባት    አሳድጎታል   እንዲያውም  የእንጨት ስራ  በሚሰራበት  ወቅት  ስራውን  ያከናውን የነበረው ለጌታ አንድ  የራሱ  መቀመጫ  ሰርቶለት ፊት ለፊቱ  አስቀምጦት  ዓይን  ዓይኑን  እያየለው እንደነበር ገድሉ ይነግረናል፡፡
     አረጋዊው    ቅዱስ     ዮሴፍ      ከእመቤታችን  በሃዘኗም    በደስታዋው   ጊዜ     አብሯት    በመሆን አገልግሏታል፡፡
    በመፅሐፍ  ቅዱስ  ላይ  ተፅፎ  እንደምናነበው ሙሴ በፈፀመው   ስህተት    (እራሱን   ከእግዚአብሔር  ጋር    አስተካክሎ ‹‹ከዚህ   ድንጋይ     ውሃ እናወጣላችኋለን››   ዘሁ.20፡10-13  በማለቱ)    አርባ  አመት  የደከመበትን     አገልግሎት     ከነአንን     እንደማይወርሳት      እና   እንደሚሞት   ቢነገረውም አገልግሎቱን ግን ቀጠለ፡፡
    እሱ   ያገለግል    የነበረው    ስለ   እግዚአብሔር ፍቅርና  ስለ   እውነት    ነበር   እንጂ   ስለ   ከነአን አልነበረም፡፡ ልክ  እንደሙሴ   ሁሉ   በብሉይ   ኪዳን የነበሩ አባቶች ከሞት  በኋላ  ወደ  ሲዖል  እንደሚወርዱ እያወቁ   በዘመናቸው  ሁሉ እግዚአብሔርን አገልግለው አልፈዋል፡፡ 
    በሐዲስ  ኪዳንም  የመጀመሪያው  ሐዋሪያ  የሆነው አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ   በስደት   ወቅት   ልጁ   ዮሳ ሔሮድስን ከኋላቸው ስለላከባቸው አራት ሰራዊት ጦር  እና  በቤተልሔምና   በአውራጃዋ  ስለተፈፀመው የእናቶች መከራና የህፃናቱ  ሲቃ  አንድም  ሳይቀር በነገራቸው ሰዓት  እመቤታችን    ቅድስት     ድንግል   ማርያም   በከፍተኛ   ደረጃ    በመደንገጧ     ጌታም  የእናቱን ድንጋጤ ተመልክቶ   ‹‹ዮሳ  አመጣጥህ  ዋጋ የሚያሰጥ   ነበር   ነገር  ግን  እናቴን  በማይገባ አስደነገጥካት በል በዳግም  ምፅአት  መጥቼ   ዋጋህን  እስክሰጥህ  ድረስ   ይችን    ድንጋይ   ተንተርሰህ  ለዘመናት  አንቀላፋ››  በማለት  ስለተናገረው   ዮሳ  ከዚያች   ደቂቃ   ጀምሮ  ነፍሱ ከሥጋው ተለይታው ሞተ፡፡
     አረጋዊው ቅዱስ የሴፍ  ይሔን  ሁሉ  በዓይኑ እያየ በቃ  ከዚህ  በኋላ  ልጄን ገሎብኛል  ማገልገል  የለብኝም ሳይል  እና  ሳሳይማረር   ታማኝ    አገልጋይ   መሆኑን አሳይቶናል፡፡
ዮሴፍ ፃድቅ ነበር፡፡ ማቴ.1፡19
     ጻድቅ  ማለት    እውነተኛ    ለእውነት    የቆመ ቅድስና ያለው በመልካም  ሥራው  የተመሰከረለት፣ ከክፉ ስራ  ሁሉ  የራቀ፣  በማንኛውም  ነገር  ነቀፋ የሌለበት ደግና ንፁህ ሰው ማለት ነው፡፡
     ነቢዩ  ሙሴ  በኃላፊነት   ለሚመራው  የእስራኤል ሕዝብ     የሚከተለውን     መመሪያ    ሰጥቶ    ነበር ‹‹የአምላክህን  የእግዚአብሔርን    ቃል   ብትሰማ   ዛሬ ያዘዝኩህን   ትዕዛዙን   ሁሉ    ብታደርግ    ብጠብቅም አምላክህ  እግዚአብሔር  ከምድር አሕዛብ ሁሉ ከፍ  ከፍ ያደርግሃል የአምላክህንም የእግዚአብሔርን ቃል  ብትሰማ  እነዚህ   በረከቶች   ሁሉ   ይመጡልሃል  ያገኙኅማል፡፡ አንተ በከተማህ ብሩክ ትሆናለህ …..›› ዘዳ.28፡1-7
     የአምላክን    ቃልና      ትዕዛዝ     ለመስማትና ለመጠበቅ  በረከትንም  ለማግኘት  በወቅቱ   የታደለው የእስራኤል  ሕዝብ   ነው፡፡   ዮሴፍም   ከዚህ   ሕዝብ መካከል የተገኘ እስራኤላዊ ፃድቅ ነበር፡፡
     የአረጋዊው  የቅዱስ  ዮሴፍ   ፃድቅነት   በምናኔ፣ በገዳም    በሚደረግ     ተጋድሎ     ሳይሆን   አብሮ በሚኖርበት     ሕብረተሰብ     ውስጥ     በሚያሳየው ደግነትና በነበረው ፍፁምነት ነው፡፡
     አረጋዊው  ቅዱስ  ዮሴፍ   በፈፀመው   ተጋድሎና በሳየው ታማኝነት እግዚአብሔር ለወዳጆቹ ባዘጋጀው እና  በሚሰጠው     ደስታና    ክብር    የፅድቅ    አክሊል ለመቀናጀት በ114 ዓመቱ  ሐምሌ  26   ቀን   በክብር አርፏል፡፡
‹‹የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት  የከበረ  ነው›› መዝ.115፡6

ጸሎቱና በረከቱ በሁላችን ላይ ይደርብን አሜን!

ቅዱስ ዮሴፍ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን 

የታመነ የከበረ የተመሰገነ ስለሚሆን ስለ ዮሴፍ የምንናገረውን ዕንወቅ እርሱ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም የሚፈጸመውን ምሥጢር አላወቀምና፡፡
አገልጋይ የሆነለት ምሥጢር ምንም እንደሆነ አላወቀም ለእርሱ ከታጨችለት ከድንግል ነቢያት ስለ እርሱ የተናገሩለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ ዘር እንዲወለድ አላወቀም በነቢይ እንደተናገረ ሕፃን ያለ አባት ከድንግል እንዲገኝ አላወቀም፡፡ኢሳ 7፡14፣9፡6-7፣ ዮሐ1፡46፡፡
ከንጹሕ ዘር የተፈጠረች ድንግል የእግዚአብሔር ማደርያ እንድትሆን አላወቀም ዘለዓለም መለወጥ የሌለበት ዳግማይ አዳም ክርስቶስ ድንግልና ካላት ገነት እመቤታችን እንዲገኝ አላወቀም፡፡ዘፍ 9፡27፣መኃ 4፡12
ፍጡራንን ሁሉ የፈጠረ ክርስቶስ ያለ ዘር እንዲወለድ አላወቀም በምድራችን ታየ ተብሎ በነቢይ እንደተናገረና ዳግመኛም ምድር ፍሬን ትሰጣለች ተብሎ እንደተናገረ ፡፡ኢሳ 32፡1-2፣ዮሐ1፡4፣ቆላ 1፡15-18፣መኃ2፡12፣መዝ 85፡12
የድንግል ሆድዋ ገፋ ያለዘር የፀነሰች ድንግልን የሆድዋን መግፋት ባየ ጊዜ የዮሴፍ ልቡ አዘነ የንጽሕት እመቤታችንን ምሥጢን ፈጽሞ መረመረና በማያውቀው ምሥጢር ጸንሳ ቢያገኛት በጽኑ አሳብ በማውጣት በማውረድ ተያዘ፡፡
ፀንሳ አገኛት በዘር የፀነሰችም መሰለው ከር የሚወለደው በግብረ መንፈስ ቅዱስ ነውና አንተም እንደምትጠራጠረው አይደለምና ዮሴፍ አትፍራ ብሎ ከእግዚአብሔር የተላከ መልአክ እስኪነግረው ድረስ፡፡

ዮሴፍም ይህን በሰማ ጊዜ ለድንግል ሰገደ ንጽሕናዋንም አመነ ነቢዩ ኢሳይያስ እነሆ ድንግል ትጸንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙም አማኑኤል ይባላል ትርሜው እግዚአብሔር ከእኛ ባሕርይ ጋር አንድ ሆነ ማለት ነው ብሎ የተናገረላት ድንግል እር እንደሆነች ዐወቀ፡፡ማቴ 1፡18-25፣ሉቃ 1፡26-39፣ኢሳ 7፡14፡፡/ሃይማኖተ አበው ዘ ቅዱስ ኤራቅሊስ ምዕራፍ 48 ክፍል 8 ቁጥር 29-35 እንን ለፃዲቁ አባታችን ለቅዱስ ዮሴፍ በዓለ እረፍት በሰላም አደረሰን በረከት ረድኤቱ አይለየን አሜን፡፡